የኢፌዴሪ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ሚያዝያ 9 ቀን 2016 ዓ.ም በሚኒስትሮች ምክር ቤት መፅደቁን ተከትሎ - ፖሊሲውን ወደ ትግበራ ምዕራፍ ለማሸጋገር የሚረዱ የቅድመ-ዝግጅት ስራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል። ከነዚህ ስራዎች መካከል አንዱ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲውን አፈፃፀም፡ ክትትልና ድጋፍ ሥርዓት የሚመራ ፍኖተ ካርታ ማዘጋጀት ሲሆን - አሁን ላይ የፍኖተ ካርታው ዝግጅት ተጠናቆ ወደ ስራ እንዲገባ ተደርጓል።